የመከላከያ ሰራዊት ህገ-መንግስታዊ መርሆዎች

         የመከላከያ ሰራዊት ህገ-መንግስታዊ መርሆዎች

  1. የሀገሪቱ የመከላከያ ሠራዊት የብሔሮች፣ የብሔረሰቦች እና የሕዝቦችን ሚዛናዊ ተዋጽኦ ያካተተ ይሆናል፡፡
  2. የመከላከያ ሚኒስትር ሆኖ የሚሾመው ሲቪል ይሆናል፡፡
  3. የመከላከያ ሠራዊት የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ከመጠበቅ በተጨማሪ በሕገ-መንግስቱ መሰረት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚሰጡትን ተግባሮች ያከናውናል፡፡
  4. የመከላከያ ሠራዊቱ በማናቸውም ጊዜ ለሕገ-መንግስቱ ተገዢ ይሆናል፡፡
  5. የመከላከያ ሠራዊቱ ተግባሩን ከፖለቲካ ድርጅቶች ወገናዊነት ነጻ በሆነ አኳኋን ያከናውናል፡፡