ሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ ሠራዊታችን ግዳጁን በብቃት እንዲፈፅም የራሱን ሚና ተወጥቷል። የምስራቅ ዕዝ ሙዚቃና ቴአትር ቡድን ኃላፊ ሌ/ኮ ጋሻው ንጉሴ

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

ግንቦት 16 ቀን 2014 ዓ.ም

ሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ ሠራዊታችን ግዳጁን በብቃት እንዲፈፅም የራሱን ሚና ተወጥቷል። የምስራቅ ዕዝ ሙዚቃና ቴአትር ቡድን ኃላፊ ሌ/ኮ ጋሻው ንጉሴ

ሠራዊቱ የሚሰጠውን ተልዕኮ በሚገባ እንዲፈፅም ሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ በግዳጅ ቀጠና ተንቀሳቅሶ የማነሳሳትና የግንባታ ስራዎችን አከናውኗል።

የምስራቅ ዕዝ ሙዚቃና ቴአትር ቡድን ኃላፊ ሌ/ኮ ጋሻው ንጉሴ እንደተናገሩት ኪነት ቡድኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ እራሱን በማብቃትና በማሻሻል ሠራዊቱ በሚገኝባቸው ግንባሮች ድረስ በመንቀሳቀስ የተጣለበትን ሃገር የማስከበር ተልዕኮውን ደስተኛ ሆኖ እንዲፈፅም ለማስቻል ሞራልና ስነ- ልቦናውን ከፍ የማድረግ ስራዎች መከናዎናቸውን ገልፀዋል።

ሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ ባቀረበው የሙዚቃ መድረክ ሠራዊቱ ደስተኛ መሆኑንና ቀጣይ ለሚሰጠው ግዳጅ ትልቅ የሞራል ስንቅ እንደገነባ በመድረኩ ተገልጿል።

ሃሰን ጀማል

ፎቶግራፍ ይቅርታ ብዙአየሁ