ድንበር በማይገድበው የህዝባዊነት ዕምነት ሌት ተቀን በመስራት የቀጣናችንን ሰላም ማረጋገጥ ችለናል ሲሉ የዘጠነኛ ዙር ሁለተኛ ታንከኛ ዋና አዛዥ ሻለቃ ቀጄላ ጨዋቃ ገለፁ።

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

የታንከኛ ክፍሉ በግዳጅ ቀጣናው የመንገድ መሠረተ-ልማት እንዲስፋፋ፣ወታደራዊ ታዛቢዎች በነፃነት ተንቀሳቅሰው ተግባራቸውን እንዲያከናውኑ፣ተሽከርካሪዎች ያለስጋት እንዲንቀሳቀሱ ተገቢ ጥበቃ ማድረግ ችለናል ያሉት ዋና አዛዡ ፣ በተቻለ መጠን የአካባቢውን ህዝብ ማህበራዊ ችግሮች እንደ ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦቶች በመሳሰሉ ለማቃለልም በትኩረት እየሠራን ነው ብለዋል።
ከፍተኛ መኮንኑ ፣ ክፍሉ የሜካናይዝድ ክፍል ቢሆንም ፣ ሁለገብ በመሆን የእግረኛን ስራ ጨምሮ እየተወጣ እንደሚገኝና ፣ የአባላቱ ጥንካሬም የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል።
የአባላቱ እና የአሽከርካሪዎቻችን የተቀናጀ እንቅስቃሴ ቀንም ሆነ ሌሊት በማንኛውም ሰዓት የሚፈጠርን ችግር ፈጥኖ በመድረስ መፍታት እንድንችል አድርጎናል ያለው ደግሞ ፣ የሁለተኛ ታንከኛ መገናኛና ስምሪት ሃላፊ የሃምሳ አለቃ ብሩክ አበራ ነው።
አስቻለው ሌንጫ
ፎቶግራፍ ብሩክ ጌታቸው